Thursday, October 4, 2012

"ወጣት እና ቤተክርስቲያን"

ምንጭ፡-የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ 

መግቢያ:
ወጣትነት ከሕፃንነት ወደ ዐዋቂነት በሚደረገው ሽግግር ወቅት አንድን ሰው ለዐዋቂነት የሚያሸጋግሩ ስነልቦናዊ፣ አካላዊ፣ ማህበራዊና አዕምሮአዊ ለውጦች የሚከናዎኑበት ጊዜ ነው፡፡ በወጣትነት ዘመን ከውስጣዊ ፈተና በተጨማሪ ውጫዊ ፈተና የራሱ የሆነ ተጽዕኖ አለው፡፡ የተሻለ የዐዋቂነት ሕይወት ለመምራት አንድ ወጣት እነዚህን ፈተናዎች በአሸናፊነት መወጣት አለበት፡፡ ቅድስት ቤተክርስቲያን በዚህ ወሳኝ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንደሚኖራት እሙን ነው፡፡ በዚህ መልኩ ልጆቿን ኮትኩታ ባሉበት ፈታኝ ዘመን ፈተናውን ተቋቁመው ማለፍ እንዲችሉ ማገዝ ከቻለች ለመንፈሳዊ ክብር ልታበቃቸው ትችላለች፡፡ በምላሹም ከወጣቶች የሚጠበቀውን መጠነ-ሰፊ አገልግሎት ማግኘት ይቻላል፡፡

ወጣትነት
"ወጣት ማለት በሰው ልጅ ሥነ ሕይወታዊ ምዕራፍ አንድን የእድሜ ክልል የሚወክል እና የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ፣ ሥነ-ልቦናዊ፣ ማሕበራዊ አቋምና ደረጃ ያለው ነው፡፡ " ማኅበረሰቦች /ሀገራት/ የየራሳቸው ከሆኑ ማኅበራዊ፣ ባሕላዊና ሌሎችም እሴቶች ጋር በተያያዘ ወጣት የሚለውን የዕድሜ ክልል ለያይተውት እናገኛለን፡፡ ለምሳሌ፡ የዓለምጤናድርጅት "Adolescent" ማለትከ10-19 ዓመት ዕድሜ ውስጥ የሚገኘውን የሕብረተሰብ ክፍል የሚወክል ሲሆን "Young peo¬ple" ማለትደግሞከ15-24 ዓመት ድረስ ያለውን ይወክላል በማለት አስቀምጧል (Hand book of pediatrics AIDS , 187)፡፡ ወጣቶችን በተመለከተ የተዘጋጁ የተለያዩ የሀገር ውስጥ ጽሁፎች በኢትዮጵያም ቢሆን ቃሉ የሆነ የዕድሜ ክልልን የሚወክል አድርገው ቢያቀርቡም ቁርጥ ያለ ነገር ለማግኘት ግን አዳጋችነው፡፡ ለምሳሌ፡- ብሔራዊ የወጣቶች ፖሊስ (National Youth Policy) ወጣትነትን ከ15- 19 ዓመት ባለው የዕድሜ ክልል ሲገድበው ከ2ዐዐ6 -2ዐ15 ድረስ እንዲያገለግል ተደርጎ የተዘጋጀው የወጣቶች የሥነ-ተዋልዶ ትግበራዊ ስልት ዶኩሜንት (Ado-lecent & Youth Reproductive Health Strategy) የዕድሜ ክልሉን ሰፋ 1ዐ- 24 ዓመት እንደ ሚያጠቃልል ይጠቁማል፡፡

Wednesday, August 22, 2012

ማህበረ ቅዱስ አሞኒ: የብፁዕ ወቅዱስ ዶ/ር አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢ...

ማህበረ ቅዱስ አሞኒ: የብፁዕ ወቅዱስ ዶ/ር አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢ...: " ለፈራሔ እግዚአብሔር ይሤኒ ደኅሪቱ፣ ወይትባረክ ዕለተ ሞቱ " " እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ፍፃሜው ያምራል፡፡ በሚሞትበትም ቀን ይከበራል " ሲራ . 1 ፡ 13 ፡፡      የብፁዕ ወቅዱስ...

Monday, August 20, 2012

Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi dead at 57


     ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) – Meles Zenawi, Ethiopia's long-time ruler who held tight control over this East African country but was a major U.S counter-terrorism ally, died of an undisclosed illness after not being seen in public for weeks, Ethiopian state television said Tuesday. He was 57. 
     Meles died Monday just before midnight after contracting an infection, state TV announced Tuesday. Hailemariam Desalegn, who was appointed deputy prime minister and minister of foreign affairs in 2010, is now in charge of the Cabinet, state TV said. 
     Meles hadn't been seen in public for about two months. In mid-July, after Meles did not attend a meeting of heads of state of the African Union in Addis Ababa, Ethiopia's capital, speculation increased that his health problems were serious. 
 
   

Thursday, August 16, 2012

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ አረፉ


ብፁዕነታቸው ያለፈው እሁድ በቅዳሴ ላይ እንደነበሩ ከውስጥ አዋቂዎች ለመረዳት የቻልን ሲሆን  ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በጠና ታመው ነሐሴ 8/2004ዓ.ም ማምሻውን ወደ ደጃዝማች ባልቻ ሆስፒታል ለህክምና ገብተው በዶክተሮች ክትትል ሲደረግላቸው ቆይተው ትላንት ለሊት ሊያርፉ ችለዋል፡፡  
የአባታችንን ነፍስ በገነት ያኑርልን አሜን፡፡

Wednesday, August 15, 2012

የእሳት ትንታግ ፍንጣሪ



የእሳት ትንታግ ፍንጣሪ
የድል ዜማ ወገን አኩሪ
የክብር ጥግ ማማ
የደስታ ውበት ቄጤማ
የመስቀሉን ኃይል ከግሸን የጸበሉን በረከት ዘግና
ይኽው አየኋ በለንደን የእሳት ልጅ እሳት ሆና
የደም አዙሪት ምሬቱ
የእሳት ትግል ሽረቱ
እየፈላባት ሐሞቷ እየታገላት ሲቃ
ታቦቷን ከራሷ ሳይሆን ከደረቷ ላይ ደብቃ
ተሻገረችው ያንን ጉድ አስለቀሰችን ነፍርቃ
ጀመረች አግዥኝ ብላ
ድንግልን በደረቷ አዝላ
ታሪክ ናት ይኽች ማሪያም ለተማጸናት በብርቱ
ልጇን ላመነ በልቡ ፍቅሯን ላሰረ በአንገቱ
እረሳችና ድካሟን የልፋት ውጤት ወርቋን
ከፍ አደረገችው ስእሏን የድንግል ማርያምን ስሟን
ግሸን ሆነች አሉ ለንደን ተቀይራ
መሰረተ ህይወት ድንግል ተዘምራ
እምነት ከጉያ ውስጥ ድንገት ፈለቀና
ሃሌ ሃሌ ሆነ ድካም ተረሳና
የእኛ ርግብ አማኝቷ
የኢትዮጵያ ልጅ መሠረቷ
ቢላላባት ያሰረችው ቢበጣጠስ መቀነቷ
ተወራርዳ አሸነፈች በጌታ እናት ባዛኝቷ

መ/ር አቡኑ ማሞ
ዋሽንግተን ዲሲ

Friday, August 10, 2012

ድንግልን ይዞ ማን አፍሮ


     ትላንት በተደረገው የሴቶች 5000 ሜትር ርቀት ኢትዮጵያ ድል የቀናት ሲሆን በውጤቱም መሠረት ደፋር አንደኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳሊያ ስታገኝ ጥሩነሽ ዲባባ ከተፍኛ የቡድን ስራ በመስራት ሶስተኛ በመውጣት የነሐስ ሜዳሊያ ማግኝት ችላለች፡፡
     መሠረት ደፋር ማሸነፏን ስታውቅ በከፍተኛ ደስታ ሆና በማልቀስ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ምስል በመያዝ እንባዋን መቆጣጠር እስከሚያቅጣት ድረስ ብርታቷ ድንግል መሆኗን ያሳየችበት ታላቅ የሩጫ መድረክ ሆኖ አምሽቷል፡፡